ለኢሬቻ ዋቀ ጉራቻ ግብር መሆኑ ነው…!
"…በዛሬው ርእሰ አንቀጼ ላይ ጠቅሼዋለሁ። ኦሮሙማው እንዴት ዐማራና ኦርቶዶክስን ከኦሮሚያም ከኢትዮጵያም እየጸዳ እንዳለ ጠቅሼላችኋለሁ። ኦሮሙማው እንዴት ሌላውን ከኦሮሚያ በኢኮኖሚ አድቅቀው፣ ተጠቃቅሰው ዘርፈው እያጸዱት እንደሆነም ጽፌላችኋለሁ። ቆይቼ ስለጥፈው አንብቡት።
"…ይህ ዜና የዛሬ ነው። ዜናው የተሠራው ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት ሊቀጳጳስ በበላይነት በሚመሩት ሚዲያ የተዘገበ ነው። አረጋዊ ካህን ዐራት ቤተሰባቸውን ጨምሮ ማንነታቸው ባልታወቁ ኃይሎች በአሰቃቂ ሁኔታ ተገደሉ ይልል ዜናው። በአንድ ቀን ለዘር ሳያስቀሩ አምስት ቤተሰብ ማረድ?
"…መልአከ/መ/ ቀሲስ ወልደ ኢየሱስ አያሌው የተባሉ በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት በሉሜ (ሞጆ) ወረዳ ቤተ ክህነት በቢቃ ደ/መ/ቅ/ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ለ41 ዓመታት ያህል ከዲቁና እስከ ደብር አስተዳዳሪነት ድረስ በትሕትና ያገለጉ አባት ማንነታቸው ባልታወቁ አካላት ከባለቤታቸውና ከሦስት ልጆቻቸው ጋር በግፍና በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸውን የሉሜ ወረዳ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት የገለጸ ሲሆን ልጃቸው ዲ/ን መልአክ ወልደ ኢየሱስም የቤተ ክርስቲያን አገልጋይ እንደነበር ተጠቅሷል፡፡ ጸሎተ ፍትሐት ሥርዓቱም የሞጆ ሉሜ ወረዳ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ሰላም ቆሞስ አባ ሰይፈ ገብርኤል ገረመው፣ የአድባራት አስተዳዳሪዎች ፣ አበው ካህናት ሊቃውንት ፣ በርካታ ምእመናን በተገኙበት በሞጆ ደ/ብ/ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን በብፁዕነታቸው መሪነት እየተከናወነ ይገኛል ይላል የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሚዲያ።
"…ለኢሬቻ ግብር ሲባል በኦሮሚያ ብቻ ሳይሆን ሰሞኑን ከዚህ የከፋ ዘግናኝ በዐማራ ክልልም ኦሮሙማው አሰቃቂ ግድያ ሲፈጽም እንሰማለን።
• ከዚህ በላይ ዘር ማጥፋት አለ እንዴ?